fbpx

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ : የገንዘብ ፖሊሲ ማሻሻያ ይፋ አደረገ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የዋጋ ንረትን ለማርገብ የሚያስችል የገንዘብ ፖሊሲ ማሻሻያ ይፋ አደረገ።
የገንዘብ ፖሊሲ ማሻሻያውን አስመልክቶ የባንኩ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
የዋጋ ንረትን በሁነኛ መልኩ እና በቀጣይነት ለመቆጣጠር የብሔራዊ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ጠንካራ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ማድረጉን ተናግረዋል።
ከውሳኔዎቹ መካከል የሀገር ውስጥ ብድር ዕድገት በ14 በመቶ ጣሪያ እንደሚገደብ ጠቅሰው፤ ይህም ሁሉም ንግድ ባንኮች የብድር ዕድገት ዕቅዳቸው በዚህ የብድር ጣሪያ መሰረት እንዲስተካከል የሚያስገድድ መሆኑን አንስተዋል።
ለመንግስት የሚሰጠው የቀጥታ ብድር ባለፈው በጀት ዓመት ከተሰጠው ከአንድ ሦስተኛ እንዳይበልጥ የፖሊሲ ውሳኔ መተላለፉንም ይፋ አድርገዋል።
ባንኮች የገንዘብ እጥረት ሲገጥማቸው ከብሔራዊ ባንክ ለሚወስዱት የብድር ፋሲሊቲ የሚከፍሉት ወለድ ከ16 በመቶ ወደ 18 በመቶ ከፍ እንዲል መወሰኑንም መግለፃቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
ቁልፍ የሆኑ የወጪ ንግዶች ላይ የተሰማሩ ላኪዎች የውጭ ምንዛሬ የማስተላለፍ ግዴታ ከዚህ ቀደም ስራ ላይ የነበረው 70/30 የድርሻ ክፍፍል ወደ 50/50 እንዲሻሻል መደረጉንም ነው የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ የገለጹት።
በውሳኔው መሰረት ከአጠቃላይ የውጭ ምንዛሬ ግኝት ውስጥ 50 በመቶውን ለብሔራዊ ባንክ እንደሚያስገቡ ተናግረዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Sign In

Register

Reset Password

Please enter your username or email address, you will receive a link to create a new password via email.